ዓለም አቀፉ ፍርድ ቤትና አፍሪቃ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 30 2007ማስታወቂያ
በአፍሪቃ መንግሥታትና በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት (ICC) መካከል ያለዉን ልዩነት ለማጥበብ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ እየተወያየ ነዉ። ትናንት በተጀመረዉ ሥብሰባ ላይ የአፍሪቃ መንግሥታት ፍርድ ቤቱ ከዓለም አቀፍነቱ ይልቅ አፍሪቃዉያንን ለመክሰስና ለመቅጣት ያለመ ነዉ በማለት ወቅሰዉታል። ፍርድ ቤቱ ከተመሠረተ ጀምሮ የከሰሳቸዉ ወይም የቀጣቸዉ በሙሉ አፍሪቃዉያን ፖለቲከኞች ናቸዉ።ኒዮርክ ሥለተያዘዉ ስብሰባ የዋሽግተን ዲሲ ዘጋቢያችን አበበ ፈለቀን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ