ውጥረት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች
እሑድ፣ የካቲት 17 2011ማስታወቂያ
የውጥረቱ መንስኤ በአንዳንዶች የአጎራባች ድንበር ግዛቶች የማንነት ጥያቄ ያስከተለው ነው የሚሉ እንዳሉ ሁሉ ይህ ውጤት እንጂ መንስኤ በማዕከላዊ መንግሥት ውስጥ የበላይነትን የማግኘት ጉዳይ እንደሆነ ይናገራሉ። የሚታየውን ችግር የየክልሉ ፖለቲከኞች እና ለክልሉ ሕዝብ ቆመናል የሚሉ አንዳንዶች ጥንቃቄ በጎደለው መልኩ የሚሰነዝሩት አስተያየት እያባባሰው መሆኑንም ያመለክታሉ። ይህ አካሄድም ወዴት ያመራ ይሆን የሚል ስጋትን አስከትሏል። DW ተጎራባች በሆኑት የአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካከል የሚታየውን ውጥረት እና ስጋት፤ ያንን ለማርገብም ሊደረጉ ስለሚገባቸው የመፍትሄ ሃሳቦች ለማንሳት የሞከረ ውይይት አካሂዷል። ዝርዝሩን ከድምጽ ዘገባው ያድምጡ።
ሸዋዬ ለገሠ
ልደት አበበ