ካሌ ስደተኞች ጣብያ የተቀሰቀሰዉ ግጭትና የኮሮና ስጋት
ዓርብ፣ ሚያዝያ 16 2012ማስታወቂያ
በርካታ ስደተኞች ወደ ታላቋ ብሪታንያ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ለመሻገር የሚጠቀሙበት የሰሜናዊ ፈረንሳይ ወደብ ከተማ በሆነችዉ ካሌ በያዝነዉ ሳምንት በፖሊስ የፀጥታ አባላትና በስደተኞች መካከል ግጭት መነሳቱ ተነገረ። ከኮሮና ተኅዋሲ ስርጭት ጋር ፈረንሳይ ዜጎችዋ በቤት ዉስጥ ተወስነዉ እንዲቀመጡ ጊዜያዊ እገዳ መጣልዋን ተከትሎ በካሌና አካባቢዋ የሚገኙ ስደተኞች ከዚህ ቀደም በሰብዓዊ ርዳታ ሰጭ ግብረሰናይ ተቋማት በኩል ይደረግላቸዉ የነበረዉ የንፅሕና መጠበቅያ ቁሳቁስና የምግብ እርዳታ በእገዳዉ ሳብያ መስተጓጎሎ የሰብዓዊ ቀዉስ እያስከተለ ነዉ። በያዝነዉ ሳምንት ረቡዕ ደግሞ ፖሊስ ካሌ ዉስጥ ሕገወጥ ናቸዉ ያላቸዉን የስደተኞች ጊዜያዊ መጠለያ ድንኳኖች ማፈራረስ መጀመሩ ትልቅ ግጭት ቀስቅሶአል።
ፖሊስ ማፈራረስ የጀመረዉ የስደተኞች መጠለያ በአብዛኛዉ ከሱዳን የመጡ ስደተኞች የሚገኙበት ሲሆን በግጭቱ በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ታዉቋል። ስደተኞች ያለበቂ ምግብ እና መጠለያ በሚኖሩበት ቦታ የኮሮና ተኅዋሲ ስርጭት ስጋት መደቀኑ ሲነገር እስካሁን አምስት ስደተኞች በተኅዋሲዉ መያዛቸዉ ታዉቋል።
ሐይማኖት ጥሩነህ
አዜብ ታደሰ
እሸቴ በቀለ