ከስዑዲ ለመመለስ የሚሹ ኢትዮጵያውያን ይዞታ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 17 2006ማስታወቂያ
ባለፉት ሳምንታት በስዑዲ ዐረቢያ ከሚገኘው ኢትዮጵያዊ ማሕበረሰብ ሲሰማና በተንቀሳቃሽ ምስል ሲታይ የነበረው ሁሉ ሰቆቃው ከተሰማቸው ታዛቢዎች ኅሊና የሚጠፋ አይመስልም። ስለደረሰው ግድያ ድብደባ፤ አስገድዶ መድፈርና ዘረፋ፤ DW ን ጨምሮ የተለያዩ መገናኛ ብዙኀን ዘግበውበታል። ከሰሞኑ እየተመለሱ ወደ ትውልድ ሀገር ስለሚገቡትም በመነገር ላይ ነው። በሌላ በኩል በዚያ የሚገኙትን ግራ ያጋባ፤ ሆኖም ተጨባጭነት የሌለው የአውሮፓ መንግሥታት ተመላሾችን ለመቀበል እንደተዘጋጁ የሚናፈሰው ወሬ፤ በእርግጥ ተጨባጭነት የሌለው መሆኑም ታውቋል። ወደ ትውልድ ሃገራቸው መመለስ ፈልገው አሁን መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙት ምን ያህል ይሆናሉ? ነቢዩ ሲራክ፤
ነቢዩ ሲራክ
ተክሌ የኋላ
ኂሩት መለሰ