በእነዚህ ሶሶት ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ሃገራቸው ወግና ባህል እድር አቋቁመው በችግርም ሆነ በደስታ መረዳዳትና መተሳሰብ ከጀመሩ ዘንድሮ 8 ዓመት ሆናቸው ። እድሩ በጀርመን ህግ መሰረት ፈቃድ ካገኘ ደግሞ 6 ዓመታት ተቆጥረዋል ። በነዚህ ጊዜያትም አቅም በፈቀደ መጠን አባላት በሃዘንም ሆነ በደስታ በእድሩ ጥላ ስር ሲረዳዱ መቆየታቸውን የእድሩ ሊቀመንበር አቶ ወርቁ በሪሁን ይናገራሉ ።
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ