የኢሕአዴግ ሹማምንት እስረኞች ይፈታሉ ካሉ ቀናት ተቆጠሩ። እስክንድር ከሚፈቱት መካከል ይሆን?
ማክሰኞ፣ ጥር 1 2010ጋዜጠኛው ከሽብር ቡድኖች ከፍተኛ አመራሮች ጋር በሕቡዕ ግንኙነት በማድረግ፣ ሁከት እና ብጥብጥ ለመፍጠር ስብሰባ በማድረግ፣ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ በመስማማት፣ ቀስቃሽ ፅሁፎችን በመፃፍ እና በማሰራጨት የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁን የመተላለፍ ክስ ተመስርቶበት ነበር የታሰረው። ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 18 አመታት ተፈርዶበት በእስር ላይ ይገኛል። ለባለቤቱ ሰርካለም ፋሲል እስክንድር ይፈታ ይሆናል የሚል ተስፋ የሰጣት ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) ሹማምንት የሰጡት መግለጫ ነው።
በመግለጫው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ "በፈጸሙት ወንጀል ምክንያት በፍርድ ቤት የተፈረደባቸውም ወይም ደግሞ በአቃቤ- ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው እና ጉዳያቸው እየተጣራ የሚገኙ የፖለቲካ አመራሮች ሆነ ግለሰቦች" ሊፈቱ እንደሚችሉ ተናግረው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖለቲካ አመራሮች እና ግለሰቦች ያሏቸው እስረኞች የሚፈቱት «ክሳቸው ተቋርጦ እንደዚሁም ደግሞ የምሕረት ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ምሕረት ተደርጎላቸው» እንደሆነም አክለዋል።
ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እንደምትለው እስክንድር "አንዳንዶች" ከተባሉት ጎራ ተመድቦ ይፈታ ይሆናል የሚል ተስፋ አሳድራ ነበር። የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን መክብብ ሸዋ አነጋግሯታል።
መክብብ ሸዋ
እሸቴ በቀለ
አርያም ተክሌ