1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

እስራኤልና ጥብቁ የስደተኞች አመራር ዘይቤዋ

ሰኞ፣ ግንቦት 27 2004

60,000 አፍሪቃውያን ስደተኞች የሚገኙባት እሥራኤል ፤ ከእንግዲህ ሌሎች እንዳይገቡ፤ የገቡትም ከመጡባቸው አገሮች ጋር በሚደረግ ስምምነት እንዲመለሱ ጥረት በማድረግ ላይ መሆንዋ ከመነገሩም ሌላ፤ ህገ ወጥ በሚባሉት ስደተኞች ላይ ጥብቅ እርምጃ ለመወሰድ ተነሳስታለች።

https://p.dw.com/p/157sn
epa03124964 African refugees wait for a job offer near the central bus station in southern Tel Aviv, Israel, 27 February 2012. Some 50,000 Africans have entered Israel in recent years, fleeing conflict and poverty in search of safety and opportunity in the relatively prosperous Jewish state. A growing number of African migrants say they were captured, held hostage and tortured by Egyptian smugglers hired to sneak them into Israel. EPA/ABIR SULTAN
ምስል picture-alliance/dpa

አንዳንድ የመንግሥት አባላት በሚሰነዝሯቸው የስደተኞችን መብዛት የማጥላላት ንግግርም ሳቢያ፤ በስደተኞች ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ቀጥሏል። ዛሬ ጧት፣ ኢየሩሳሌም ውስጥ፣ 18 የኤርትራ ተወላጆች በሚገኙበት በአንድ አሮጌ ባለ 2 ፎቅ ህንጻ ላይ ሆን ተብሎ በተወሰደ የማቃጠል እርምጃ 4 ኤርትራውያን የመቁሰልና በጢስ የመታፈን አደጋ ደርሶባቸው ወደ ሀኪም ቤት መወሰዳቸው ተነግሯል። እሥራኤል ለምንድን ነው በስደተኞች ላይ ጠጣር እርምጃ የምትወስደው? ፤ በዚያው በእሥራኤል ፣ የመንግሥት ያልሆነውን ፤ የአፍሪቃ ስደተኞች የዕድገት ማዕከል የተሰኘውን ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ባዩን ወደ እስቱዲዮ ከመግባታችን በፊት በስልክ አነጋግሬአቸው ነበር።

ተክሌ የኋላ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ