1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያ-የአነሳ ብሔረሰቦች መብትና ወቀሳዉ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 1 2004

ተወካዮቹ እንደሚሉት የአካባቢያዊ መስተዳድሮች ባለሥልጣናት የማሕበረሰቡ አባላትን ይበድላሉ፥ከሥራ ያፈናቅላሉ፥ የማሕበረሰቡ አባላት በብዛት በሚኖርበት አካባቢም የመሠረተ ልማት አዉታር እንዳይዘረጋ ያከላክላሉም

https://p.dw.com/p/RqZR


የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግሥትና የክክልል መስተዳድሮች ኢትዮጵያዊነታችንን እያጠራጠሩን፥ ሕገ-መንግሥታዊ መብታችንንም እየጣሱብን ነዉ በማለት የተለያዩ ማሕበረሰብ ተወካዮች አማረሩ።የዳጣ፥ የዱቤና የሌሎች አነሳ ማሕበረሰብ ተወካዮች እንደሚሉት መብታቸዉን ለማስከበር ላለፉት ሃያ አመታት ቢሟገቱም እስካሁን መፍትሔ አላገኙም።ተወካዮቹ እንደሚሉት የአካባቢያዊ መስተዳድሮች ባለሥልጣናት የማሕበረሰቡ አባላትን ይበድላሉ፥ከሥራ ያፈናቅላሉ፥ የማሕበረሰቡ አባላት በብዛት በሚኖርበት አካባቢም የመሠረተ ልማት አዉታር እንዳይዘረጋ ያከላክላሉም።የኢትዮጵያ የፌደሬሽን ምክር ቤት ጉዳዩ እየተጠና ነዉ ባይ ነዉ።ታደሰ እንግዳዉ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።

ታደሰ እንግዳዉ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ