1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያ፤ የባለሥልጣናት መሻርና ምክንያቱ

ረቡዕ፣ ግንቦት 7 2005

አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ሥልጣን ባለፈዉ መስከረም ከያዙ ወዲሕ ሚንስትሮች ከሥልጣን ሲወገዱ አቶ ሐይሉ ሁለተኛዉ ናቸዉ።።አቶ መላኩን ጨምሮ ባንድ ጊዜ በርካታ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከሥልጣን ሲወገዱ ወይም ሲከሰሱ ደግሞ የሰሞኑ የመጀመሪያዉ ነዉ።

https://p.dw.com/p/18YDo
Aerial view of Addis Ababa © derejeb #42996737
ምስል derejeb/Fotolia

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ የሐገሪቱን የፍትሕ ሚንስትር፥ የገቢዎችና የጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ሐላፊ፥ ምክትላቸዉንና ሌሎች ባለሥልጣናትን ከየሥልጣናቸዉ አስወግዷል። መገናኛ ዘዴዎች እንደዘገቡት የፍትሕ ሚንስትር አቶ ብርሐን ሐይሉ ከሥልጣን የተነሱት አቅም አንሷቸዋል በሚል ምክንያት ሲሆን፥ የጉምሩክ ሐላፊ አቶ መላኩ ፈንታ እና የበታቾቻቸዉ ደግሞ በሙስና ተዘፍቀዋል በሚል ነዉ።አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ሥልጣን ባለፈዉ መስከረም ከያዙ ወዲሕ ሚንስትሮች ከሥልጣን ሲወገዱ አቶ ሐይሉ ሁለተኛዉ ናቸዉ።ከዚሕ ቀደም የአቅም ግንባታ ሚንስትር የነበሩት አቶ ጁኔዲን ሳዶ ከስልጣን ተወግደዋል።አቶ መላኩን ጨምሮ ባንድ ጊዜ በርካታ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከሥልጣን ሲወገዱ ወይም ሲከሰሱ ደግሞ የሰሞኑ የመጀመሪያዉ ነዉ።አልበዛም ወይ? ምክንያቱስ  በርግጥ የአቅም እጦት፥ ሙስና፥ ዋልጌነት ወይስ ሌላ፥-የምሥራቅ አፍሪቃና የመካከለኛዉ ምሥራቅ ጉዳይ ፖለቲካ ተንታኝ አቶ ዩሱፍ ያሲንን በስልክ ጠይቄያቸዋለሁ።

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ