ሳይንስ
ኢትዮጵያውያት ተመራማሪዎች
ረቡዕ፣ የካቲት 4 2012ማስታወቂያ
ከጎርጎሪዮሳዊው 2015 ዓ,ም ጀምሮ የተባበሩ መንግሥታት ድርጅት በወሰነው መሠረት በሳይንስ ዘርፍ የተሠማሩ አዋቂ እና ወጣት ሴቶች በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ይታሰባሉ። ይህ የተደረገበት ዋና ዓላማም ሴቶች በሳይንስ ዘርፍ የሚኖራቸው ተሳትፎ እና ወደምርምሩ የመግባት እኩል ዕድል እንዲኖራቸው ለማበራታታት ነው። እስካሁን የተሳካላቸው ጥቂትም ቢሆኑ ሴቶች በየወጡበት ማኅበረሰብ በፆታቸው ምክንያት የሚያጋጥማቸውን ተጽዕኖ ተቋቁመው በተለያዩ የምርምር ዘርፎች መሠማራታቸው አዳጊ ሴቶችን የማነቃቃት ሚና እንዳለው ብዙዎች ያምናሉ። ትናንትም ዕለቱ ለስድስተኛ ጊዜ በዓለም ደረጃ ታስቧል። የዕለቱ ሳይንስና ቴክኒዎሎጂ መሰናዶ ሁለት ኢትዮጵያውያን ሴት ተመራማሪዎችን እንግዳው አድርጓል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሰ