ኢትዮጵያዊዉ የቦን ዩንቨርስቲ ተማሪና ተሞክሮዉ
እሑድ፣ ግንቦት 27 2009ማስታወቂያ
እንዳለዉ በዚሁ የራድዮ ጣቢያችን በሚገኝበት በቦን ከተማ ነዋሪ ከሆነ ዘጠኝ ወር ሞላዉ። እንዳለዉ የጀርመን የአካደሚ ልውውጥ አገልግሎት « DAAD »በሰጠዉ የትምህርት እድል በቦን ዩንቨርስቲ በምድር ወገብ አካባቢ ባሉ ሃገራት ትኩረት የሚያደርግ በግብርና እና የተፈችሮ ሃብት አስተዳደር ላይ የተመሰረተ የሁለተና ዲግሪ ትምህርቱን እየተከታተለ ነዉ። ባለፈዉ ሚያዝያ ወር በርሊን ላይ ለሁለት ቀናት በተካሄደዉ የቡድን 20 ቅድመ ስብሰባና አዉደ-ጥናት ላይም ተካፋይ ነበረ። በቅርቡ ለትምህርታዊ ጉብኝት በሚማርበት በቦን ዩንቨርስቲ በኩል የኢራንን ዋና መዲና ቲህራንንም ጎብኝቶ ነዉ የተመለሰዉ። እንዳለዉ አበባ በጀርመን የመጀመርያ ወራቶች ቆይታዉንና ስለትምህርቱ በጥቂቱ ጠይቀነዋል። ሙሉዉን ቅንብር ይከታተሉ።
አዜብ ታደሰ
ልደት አበበ