1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያና አከራካሪው የቡና ምርት ግብይት ደምብ

ረቡዕ፣ መጋቢት 30 2001

የኢትዮጵያ መንግስት የስድስት ታዋቂ ቡና ገዢዎችና አከፋፋዮችን ፈቃድ ከሰረዘ በኋላ አሁን የኢትዮጵያ መንግስት የቡናውን ምርት ራሱ እንደሚሸጥ አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/HSzE
ምስል AP

ስለዚሁ ብዙ ማከራከር ስለያዘው አዲሱ ደምብ ወኪላችን ጌታቸው ተድላ የኮምዩኒኬሽን ሚንስትር አቶ በረከት ስምዖንን እና የኦሮሙያ ቡና ገበሬዎች ህብረት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ መስቀላን አነጋግሮዋል። ይሁንና፥ ይኸው መንግስት የቡናውን ምርት ራሱ ለመሸጥ ያወጣው ደምብ የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተቀባይነት እንዳይጎዳ አንዳንድ በዩኤስ አሜሪካና በካናዳ የሚገኙ የቡና አስመጪና አከፋፋይ ኩባንያዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ጌታቸው ተድላ/አበበ ፈለቀ/አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሐመድ