«አክሰስ ሪል ኢስቴት» በደል አደረሰብን ያሉ ወገኖች ጉዳይ፣
ሐሙስ፣ መጋቢት 26 2005ማስታወቂያ
«አክሰስ ሪል ኢስቴት» ከተባለ የከተማ ቤቶች ሠሪና ሻጭ ኩባንያ፣ ቤት ለመግዛት የተመዘገቡ ወገኖች፣ በደል ተፈጸመብን ሲሉ ምሬታቸውን መግለጻቸው ተነገረ።
ተበደልን ያሉት ወገኖች፤ ኩባንያው በገባው ውል መሠረት ፤ ቤት ሊያስረክበን ቀርቶ፣ በባንክ የሂሳብ ሰነድ(አካውንት) ብር ስለሌለ፣ ገንዘባችን ቀልጦ ቀረ ሲሉ አምርረዋል።
ብሶታቸውን ያሰሙት ወገኖች፤ የተጠቀሰው የከተማ ቤቶች ሠሪና ሻጭ ኩባንያ ዋና ሥራ አሰኪያጅ፣ በሀገር ውስጥ ስለሌሉ፣ መልስ የሚሰጣቸው በመጥፋቱ፤ ኮሚቴ አዋቅረው ጉዳዩ ወደ ህግ እንዲያመራ የሚያደርጉ መሆናቸውን ም ገልጸዋል።
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ተክሌ የኋላ
አርያም ተክሌ