ትኩረት በአፍሪቃ
ቅዳሜ፣ ኅዳር 20 2007ማስታወቂያ
በመሪዎቿ ብሎም ነፍጥ ባነሱ አማፂያን ተደጋጋሚ በደል የሚደርስባት አፍሪቃ ዛሬም በተለያዩ ስፍራዎቿ በደሉ አልተቋረጠም። የዛሬው ትኩረት በአፍሪቃ ዝግጅት አፍሪቃ ውስጥ በወታደሮች እና በአማፂያን ስለሚደፈሩ ሴቶች የሚቃኝ ነው። በአስገድዶ መደፈር ጥቃት የደረሰባቸው ሰለባዎችን ለማከም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፥ ቡካቩ ውስጥ የፓንዚ ሐኪም ቤትን መስርተው ከፍተኛ እንቅስቃሴ ያደረጉት የኮንጎው ተወላጅ ዴኒስ ሙክዌጌ ዘንድሮ የ2014 የሳካሮቭ ተሸላሚ ለመሆን በቅተዋል። በሕክምና ሙያ የተሰማሩት ዴኒስ ሙክዌጌ ሽትራስቡግ ከተማ በሚገኘው የአውሮጳ ህብረት ምክር ቤት በተዘጋጀላቸው የሽልማት ስነስርዓት ከህብረቱ የምክር ቤት ፕሬዚዳንት ማርቲን ሹልስ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል። የጋዜጦች አምድ ግጭት በሊቢያ፣ የማዳጋስካር ተስቦ፣ አምባገነን መሪዎች እና ባለቤቶቻቸው በአፍሪቃ የተሰኙ እና ሌሎች ዘገባዎችንም አካቷል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
ማንተጋፍቶት ስለሺ