1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቱስክ፤ ብሪታንያ ከኅብረቱ የምትወጣበት ቀነ ቀጠሮ ይራዘም

ረቡዕ፣ መጋቢት 18 2011

ብሪታንያ ከአውሮጳ ህብረት አባልነት ለመውጣት የተስማማችበት የብሬግዚት ውል የብሪታንያ ፖለቲከኞችን ማወዛገቡ ቀጥሏል። በሌላ በኩል ብሪታንያ ከህብረቱ እንድትወጣ ከሚጠይቀው ከዛሬ ሁለት ዓመት ተኩሉ የህዝበ ውሳኔ ውጤት በኋላ በርካታ ብሪታንያውያን ወደ ሌሎች ሀገራት እየፈለሱ ነው። የመፋቸዉ ቀነ ቀጠሮ ይራዘም ጥያቄ ቀርቦአል።

https://p.dw.com/p/3FlZ0
Donald Tusk und Michel Barnier im EU Parlament in Strasbourg
ምስል Reuters/V. Kessler

የአዉሮጳ ኅብረት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ቱስክ፤ ለኅብረቱ ፓርላማ ላይ ባደረጉት ንግግር ብሪታንያ ከአዉሮጳ የምትወጣበት ቀነ ቀጠሮ እንዲራዘም አስታወቁ። ቱስክ በንግግራቸዉ የብሪታንያን ከአዉሮጳ ኅብረት መዉጣት የሚቃወሙና፤ ሁለተኛ ሕዝበ ዉሳኔ እንዲካሄድ ጥያቄ የሚያቀርቡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የብሪታንያ ዜጎችን ቸል ማለት አይቻልም ሲሉ ለፓርላማዉ አባላት ተናግረዋል። ኅብረቱ ብሪታንያ ከአዉሮጳ ኅብረት የምትወጣበትን እስከ ሚያዝያ 4 ድረስ ማራዘሙ ይታወቃል። ዛሬ ምሽት ላይ  የብሪታንያ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት በብሪግዚት ዉል ላይ ድምፅ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን በተሰበሰቡ የቅድምያ መዘርዝር መረጃዎች መሰረት መወሰኛ ምክር ቤቱ አብላጫ ድምፅ ላይሰጥበት ይችላል ተብሎአል። የፊታችን አርብ ብሪታንያ ከየአዉሮጳ ኅብረት አባልነት ትወጣለች ተብሎ የተያዘዉ የመጀመርያ ቀነ-ቀጠሮ ነዉ።  

Belgien, EU-Gipfel in Brüssel
ምስል Getty Images/S. Gallup

 

አዜብ ታደሰ 

ኂሩት መለሠ