በካይሮ ከተሞች የቀጠለው የሕዝብ ዓመፅ
ሰኞ፣ ኅዳር 11 2004ማስታወቂያ
በሳምንቱ መጨረሻ በታህሪር አደባባይ በተለይም በአሌክሳንድሪያ በተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በርካቶች መቁሰላቸው እየተገለፀ ነው።የግብፅ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዛሬ እንደገለፀው ትናንት በታህሪር አደባባይ በፀጥታ አስከባሪዎች እና በሰልፈኞች መካከል በተደረገው ፍልሚያ የሞቱት ቁጥር 20 እንደሆኑ ነው። ከሺ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል። ከአለፉት 2 ቀናት ጋር ሲነፃፀር ዛሬ አመፁ ጋብ ብሏል። የቀድሞው የግብፅ መሪ ሆስኒ ሙባረክ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ወታደራዊው ኃይል ስልጣኑን ይዞ ሰንብቷል። ብዮርን ብላሽከ ሰሞኑን በግብፅ ስላለው ሁኔታ ዘግቧል።
ልደት አበበ
አርያም ተክሌ