በእስር ላይ የሚገኙ 528 ተጠርጣሪዎች በይቅርታ ሊፈቱ ነው
ሰኞ፣ ጥር 7 2010ማስታወቂያ
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ጌታቸው አምባዬ ኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በቅርቡ ያካሄደውን ስብሰባ ሲያጠናቅቅ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት እነዚህን ጨምሮ በአጠቃላይ በእስር ላይ የሚገኙ 528 ተጠርጣሪዎች በይቅርታ ይፈታሉ ብለዋል፡፡ የመጀመሪያው ዙር የይቅርታ ሂደት እስከሚቀጥለው ሁለት ወራት እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡
በክልሎች ጭምር ይቀጥላል በተባለው የይቅርታ እና ክስ የማቋረጥ ሂደት እስካሁን ተጠቃሚ የሆኑት በፌደራል ደረጃ እና በደቡብ ክልል ያሉ ተጠርጣሪዎች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ የጠቅላይ አቃቤ ህጉን መግለጫ የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሃንስ ገብረእግዚያብሔር የላከውን ዝርዝር ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ፡፡
ዮሃንስ ገብረእግዚአብሔር
ተስፋለም ወልደየስ
አርያም ተክሌ