1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

84 የነብርና አንድ የአዞ ቆዳ ተቃጠለ

ሰኞ፣ ነሐሴ 18 2012

ሰሞኑን በተለያዩ ጊዜዎች በህገወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጡ ሲሉ የተያዙ14 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ 84 የነብርና አንድ የአዞ ቆዳ  መቃጠላቸውን አቶ ጋሻው ተናግረዋል፡፡ለከማቃጠል ለክልሉ ልማት መዋል አይችሉም ነበር ወይ ተብለው ከዶይቼ ቬለ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ዓለም አቀፍ ህጉ እንደማይፈቅድ አቶ ጋሻው ገልፀዋል፡፡

https://p.dw.com/p/3hQVP
Umwelttag
ምስል AP

14 ሚሊዮን ብር የተገመተ 84 የነብርና አንድ የአዞ ቆዳ ተቃጠለ

              
በአማራ ክልል ህገወጥ የዱር እንስሳት አደን እየተስፋፋ መምጣቱን የአካባቢው ነዋሪዎች አመልክተዋል፣ 14 ሚሊዮን ብር የሚገመት ህገወጥ የነብር ቆዳ ሰሞኑን መቃጠሉን የአማራ ክልል አካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡ በአማራ ክልል አካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እሸቱ ለዶይቼ ቬለ አንዳሉት ህገወጥ የዱር እንስሳት አደን አሁን አሁን እየሰፋ መጥቷል፡፡ ሰሞኑን በተለያዩ ጊዜዎች በህገወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጡ ሲሉ የተሰበሰቡ 14 ሚሊዮን ብር ማውጣት የሚችል 84 የነብርና አንድ የአዞ ቆዳ  መቃጠላቸውን አቶ ጋሻው ተናግረዋል፡፡ ለምን ተቃጠሉ ለክልሉ ልማት መዋል አይችሉም ወይ ሲል ከዶይቼ ቬለ ተጠይቀው ዓለም አቀፍ ህጉ እንደማይፈቅድ አቶ ጋሻው ገልፀዋል፡፡ አደን ህገወጥ ቢሆንም አንዳንዴ የሚፈቀድበት ሁኔታ መኖሩን ጠቁመው ይህም የሚሆነው እንስሳቱ እድሜያቸው ሲያረጅ መሆኑን አስታውቀው ለውጪ አዳኞች የሚፈቀድበት ሁኔታ ይኖራል ብለዋል፡፡የምዕራብ ጎንደር ነዋሪው ሙሉጌታ ተመስገን ለዶይቼ ቬሌ በስልክ እንደተናገሩት ከአልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ በርካታ የዱር እንስሳት በህገወጥ መንገድ ይታደናሉ፤አደን በስፋት በአካባቢው ይዘወተራል ብለዋል፡፡በሰሜን ብሔራዊ ፓርክም ተመሳሳይ የህገወጥ አደን መኖሩን የአካባቢው ነዋሪዎች አመልክተዋል፡፡ በተለይ የነብር ቆዳ በስፋት በህገወጥ መንገድ እየተሸጠ በመሆኑ የእንስሳው ዝርያ እንዳይጠፋ ስጋታቸውን ገልፀዋል፡፡ችገሩን ለመከላከል ጥበቃ ማድረግ ብቻውን መፍትሔ እንዳልሆነ ያመለከቱት አቶ ጋሻው ህብረተሰቡ የዱር እንስሳትን ጠቀሜታ እንዲያውቅና እንዲንከባከብ የማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እየተከናወነ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ 

ዓለምነው መኮንን 
ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ