በቤተ-ሙከራ ሰዉ ሊፈጠር ነዉ
ሐሙስ፣ ጥቅምት 8 2005ማስታወቂያ
የጃፓን ሳይንቲስቶች በቤተ-ሙከራ ሰዉ መስራት ወይም መፍጠር ከሚችሉበት ደረጃ መድረሳቸዉን አስታወቁ።የኪዮቶ ዩኒቨርስቲ ባልደረቦች እንደሚሉት ከዚሕ ቀደም የወንድ የዘር ፍሬን ሕዋስ አሁን ደግሞ የሴት የዘር እንቁላል ሕዋስ መስራት ችለዋል።ተመራማሪዎቹ እንደሚሉት አዲሱ ግንታቸዉን በአይጦች ላይ ሞክረዉ የተሳካ ዉጤት አግኝተዋል።የምርምሩን ዉጤት አንዳድ ሳይኒስቶች መዉለድ ለማይችሉ ሰዎች ጥሩ መፍትሔ፥ ለሕክምና ሳይንስ ጠቃሚ እድገት በማለት ሲያደንቁት፥ ሌሎች ግን የሰዉ ልጅ ተፎጥራዊ ባሕሪ የሚያዛባ በማለት አኪያኪሰዉታል።የለንደንዋ ወኪላችን ሐና ደምሴ ዝር ዝር ዘገባ ልካልናለች።
ሐና ደምሴ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ