የጀርመንዋ መራሂተ መንግሥት
ማክሰኞ፣ ነሐሴ 17 2008ማስታወቂያ
ይህ የሜርክልን የማይረሳ ጥሪ ዉሳኔና ዓለም ላይ የጀርመንን ገጽታ ቀይሮታል። አብዛኞች በዚህ ርምጃ ተገርመዋል፤ ተደንቀዋል። በሌላ በኩል ይህ ጥሪያቸዉ በመራሂተ መንግሥትዋ ላይ ተችዎችን አስነስቶባቸዋል። ሜርክል ስደተኞችን ተቀበሉ አስተናግዱ ብቻም ሳይሆን አንድ ላይ ሆነን ችግሩን እንወጣዋለን፤ በአንድ ላይም እንፈታዋለን ሲሉ ነዋሪዉን አበረታተዉም ነበር። ይህ በሰብዓዊነቱ ተወዳዳሪ የማይገኝለት የሜርክል ርምጃ የ 21ኛዉ ክፍለ ዘመን ክስተት ነዉ። እንድያም ሆኖ አሁን ከአንድ ዓመት በኋላ በተከተለዉ ችግር አብረን እንወጣዋለን የሚለዉ የሜርክል ጥሪ ጥያቄ ዉስጥ የገባ ይመስላል። በርግጥ እንወጣዉ ይሆን በሚል ርዕስ የዶቼ ቬለዉ አንድርያስ ቤከር የዘገበዉን የበርሊኑ ወኪላችን ተርጉሞ ልኮልናል።
አንድርያስ ቤከር / ይልማ ኃይለሚካኤል
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ