ሻኪሶ ከሥራ ማቆም እስከ አደባባይ ተቃውሞ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 30 2010ማስታወቂያ
በሻኪሶ የወርቅ ማዕድን ማውጫ እና በአቅራቢያው በሚገኘው ክብረ-መንግሥት ከተማ ነዋሪዎች፦ ከወርቅ ማዕድን ማምረቻው የሚወጣው ዝቃጭ ለጤናችን ችግር ፈጥሮብናል ሲሉ ለሦስት ቀናት የሥራ እንቅስቃሴ አቁመዋል። በአካባቢው ከትናንት ጀምሮ በሥራ ማቆም የጀመረው ተቃውሞ ዛሬ ወደ ግጭት መቀየሩን እና አስለቃሽ ጢስ መተኮሱን ሁለት ሰዎችም በከባድ ኹኔታ መቁሰላቸውን ፓርቲያቸው በአካባቢው ተጠሪ እንዳለው የገለጡት የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል። ሌላ የአካባቢው ነዋሪን እና የሻኪሶ ከንቲባን በማነጋገር ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ቀጣዩን ዘገባ ከአዲስ አበባ ልኮልናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ