ስደተኞችና አዉሮጳ
ረቡዕ፣ ጥቅምት 19 2007ማስታወቂያ
የሜድትራንያን ባሕር አቋርጠዉ ወደ አዉሮጳ ለመግባት የሚሞክሩና የገቡ ስደተኞች የሚገጥማቸዉ ችግር ሥለሚቃለልበት ሁኔታ የተወያየ አዉደ ጥናት ብራስልስ-ቤልጅግ ዉስጥ ተደርጓል።አዉደ ጥናቱ የተደረገዉ ባለፈዉ ዓመት ከሰወስት መቶ የሚበልጡ በአብዛኛዉ ኤርትራዉያን ስደተኞች ኢጣሊያ ደሴት ላምፔዱዛ አጠገብ ባሕር ዉስጥ ሰጥመዉ ካለቁ በሕዋላ ኢጣሊያ የጀመረችዉን ነብስ አድን ዘመቻ እደምታቋርጥ በማስጠንቀቋ ነዉ።በአዉደ ጥናቱ ላይ የተካፈሉ የተለያዩ ድርጅቶችና ተቋማት ተጠሪዎች የአዉሮጳ መንግሥታት ሥደተኞቹን ከአደጋ ለማዳንና ለመርዳት እንዲጥሩ ጠይቀዋል።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ