ሳዉዲ የሚሰቃዩ ዜጎች ጉዳይ ያነሳዉ ተቃዉሞ
ሐሙስ፣ ኅዳር 5 2006ማስታወቂያ
በጀርመን የሳዉዲ ቆንስላ በሚገኝበት ስፍራ በሃዘንና ቁጣ መሰባሰባቸዉን የገለፁት ሰልፈኞች ሳዉድ አረቢያ ኢትዮጵያዊ እህቶቻችንን መግደልና መድፈር፤ ወንድሞቻችን ማሰቃየትና መግደል አቁሚ የሚል መፈክራቸዉን ሲያሰሙ አርፍደዋል። ሰልፉ በጀርመን ሰዓት ከቀትር በፊት የጀመረ ሲሆን ከቆንስላዉ የሳዉዲ ተወካዮች ወጥተዉ ደብዳቤ ካልተቀበሏቸዉ አካባቢዉን እንደማይለቁ የገለፁት እነዚህ ወገኖች በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን ሊደረግ የማይገባዉ የጭካኔ ተግባር ያሉትን ድርጊትም እንዴት ያለ ምግባርና እንዴት ያለ ሰብዓዊነት ነዉ ሲሉም ኮንነዋል። ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዷ የሆኑት ወይዘሮ አሳየሽ ታምሩ ሮይሽልን ስለተካሄደዉ ሰልፍ በስልክ አነጋግሬያቸዋለሁ፤
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ