ሰማያዊ ፓርቲ የጠራዉ ሰላማዊ ሰልፍ
ዓርብ፣ ግንቦት 23 2005ማስታወቂያ
ፓርቲዉ በሀገሪቱ ዉስጥ አሉ ያላቸዉ አፋኝ ነገሮች እንዲሻሻሉ ለመንግስት ተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረቡን በመጠቆም ፤ በሰልፉ የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞች፤ በሃይማኖታዊ ጉዳይ በማንሳታቸዉ የታሠሩት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ የመፍትሄ አፈላላጊዎች እንዲፈቱ ለመጠየቅ መዘጋጀቱን ገልጿል። የፓርቲዉ ሊቀመንበር ኢንጂኒየር ይልቃል ጌትነት ለዶቼ ቬለ እንደገለፁት እሁድ ዕለት በሚካሄደዉ የሰላማዊ ሰልፍ ከመቶ ሺህ ህዝብ በላይ ይሳተፋል የሚል ግምት አለ። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ባለፈዉ ሳምንት ይካሄዳል ተብሎ ሲጠበቅ ወደዚህ ሳምንት ስለተሻገረዉ ሰላማዊ ሰልፍስቱዲዮ ከመግባታችን አስቀድሞ በስልክ ጠይቄያቸዋለሁ።
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሰ