ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ የሰየሙዋቸው ካርዲናሎች
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 27 2007ማስታወቂያ
ከ80 ዓመት እድሜ በታች ከሆኑት ተሰያሚ 20 ቄሶች መካከል 15ቱ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ፤ በሞት አልያም በተለያዩ ምክንያቶች ቦታቸዉን ቢለቁ ሊተኩዋቸዉ እንደሚችሉ ተዘግቧል። ጳጳሳቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከኢጣልያ፣ ከፈረንሳይ፣ ከፖርቹጋል፣ ከኒዉዚላንድ፣ ከቬትናም፣ ከሜክሲኮ፣ ከማይናመር፣ ከታይላንድ፣ ከኡራጉዋይ፣ ከስፔን፣ ከፓናማ፣ ከካፕቬርዴ እና ከቶንጋ የተዉጣጡ መሆናቸዉ ተመልክቶአል። ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ፤ አንድ ኢትዮጵያዊ ጳጳስን ጨምሮ፤ ሶስት ጳጳሳትን ከአፍሪቃ ሰይመዋል። አዲስ የተሰየሙት ካርዲናሎች ሚና ምንድን ነው? ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን የተሰየሙትስ ጳጳስ ማን ናቸው፤ ሮም የሚገኘው ዘጋቢያችን ተክለ እዝጊ ገብረየሱስን በስልክ አነጋግረንዋል
ተክለ እዝጊ ገብረየሱስ
ልደት አበበ