1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሚዲያ እና ዴሞክራሲ ላይ ያተኮረው ውይይት

ሰኞ፣ መጋቢት 2 2011

የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅ ጃዋር መሐመድ፣ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ጋዜጠኛው ሲሳይ አጌና ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት በመገናኛ ብዙኃን እና በዴሞክራሲ ላይ ያተኮረ ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተካሒዷል።

https://p.dw.com/p/3Eoqf
Äthiopien Diskussion Medien und Demokratie in Addis Abeba
ምስል DW/Y. Gebregziabher

ሚያዲያ እና ዴሞክራሲ ላይ ያተኮረው ውይይት

የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅ ጃዋር መሐመድ፣ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ጋዜጠኛው ሲሳይ አጌና ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት በመገናኛ ብዙኃን እና በዴሞክራሲ ላይ ያተኮረ ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተካሒዷል።

በውይይቱ ጃዋር መሐመድ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን የከፋ አደጋ አለማድረሳቸውን ተናግሯል። ጃዋር "ምኅዳሩ ከልክ በላይ በሰፋበት፣ ይኸን ምኅዳር ግልፅ የሆነ ሕግጋት እና አሰራር በመንግሥትም ሆነ በሚዲያው ባልተቀመጠበት ሒደት ውስጥ እስካሁን እኔ የማያቸው አብዛኞቹ ሚዲያዎች የሕዝባዊ ግጭትን በመንግሥት እና በአገር ደሕንነት ላይ አደጋ የሚያደርስ አሰራር ውስጥ" አልገቡም ሲል ተናግሯል።

Äthiopien Diskussion Medien und Demokratie in Addis Abeba
ምስል DW/Y. Gebregziabher

በመድረኩ ተሚሰራበት ተቋም ጋር በተያያዘ ተቃውሞ የገጠመው ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና "የመንግሥት ባለሥልጣናት አካባቢ መረጃ ለማግኘት የሚደረጉ ዝግ ኹኔታዎች አሉ። እነዚያ ኹኔታዎች የሚሻሻሉ ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ መልኩ ሐሳብን የመግለፅ ነፃነት በከፍተኛ ደረጃ ተከፍቷል።  ይኸ ነፃነት ግን ወደ መጥፎ አቅጣጫ እየሔደ መሆኑ ማሳሰቡ ተገቢ ይመስለኛል" ብሏል።

በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በበኩላቸው "በጋዜጠኝነት እና በአራማጅነት መካከል ትክክለኛ መስመር እና ድንበር ወጥቶ የሚሔዱበት ኹኔታ በውስንነት የሚታይ ነው" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

ተስፋለም ወልደየስ

እሸቴ በቀለ