1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሕገ-ወጥ የተባሉ ቤቶች ፈረሳ በዓዲግራት 

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 1 2011

በሕጋዊ መንገድ የገነባናቸው መኖርያ ቤቶቻችን መንግስት እያፈረሰብን ነው ሲሉ በዓዲግራት ከተማ ዙርያ የሚገኙ ነዋሪዎች ቅሬታቸው ገለፁ፡፡ ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ እየተካሄደ ባለው ቤቶች የማፍረስ ዘመቻ ከ300 በላይ ቤቶች መፍረሳቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ለዲደብሊው ተናግረዋል፡፡

https://p.dw.com/p/3GWbE
Äthiopien Stadtansicht Mekele
ምስል DW/M. Hailessilasie

በዓዲግራት ዙርያ የሚገኙ ቀርሰበርና ማይመሳኖ የተባሉ አካባቢዎች ለአመታት ኑሯቸው ያደረጉ ቅሬታ አቅራቢዎች እንደሚሉት በቅርቡ እየፈረሱ ያሉት መኖርያ ቤቶች ሕጋዊ ሰነድ ያላቸው መሆናቸው ይገልፃሉ፡፡ በ2007 ዓ.ም በአካባቢው የነበሩ ሕጋዊ ሰነድ ያልነበራቸው ቤቶች መፍረሳቸውን የሚገልፁት ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች በወቅቱ ሕጋዊ የተባሉ ቤቶች አሁን ሕጋዊ አይደሉም' ተብሎ ያለ አግባብ ንብረታችን እየወደመ ነው ይላሉ፡፡እስካሁን ከሶስት መቶ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን የሚገልፁት ነዋሪዎቹ በነባር ይዞታ ላይ የተገነቡ መኖርያዎችንም የማፍረስ ዘመቻው አካል ሆነዋል ይላሉ፡፡


ሚሊዮን ኃይለስላሴ 


አዜብ ታደሰ 
ነጋሽ መሐመድ       

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ