ለይግባኝ ውሳኔው ሌላ ቀጠሮ መስጠቱ
ረቡዕ፣ መጋቢት 18 2005ማስታወቂያ
የቀድሞዉ የመድረክ ከፍተኛ አመራር አባል እነ አቶ አንዷለም አራጌ ባቀረቡት ይግባኝ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ ቀጠሮ ይዞ የነበረው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ ። ተከሳሾቹ ዛሬ ባለመቅረባቸው ችሎቱ ለመጋቢት 30 ፣ 2005 አም ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ። የጋዜጠኛ ተመሰገን ደሳለኝን የመከላከያ ምስክር ለማዳመጥ ትናንት የተሰየመው ችሎትም በተተከሳሹ ጥያቄ ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል ። ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ አለው ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ