አንዳርጋቸው ጽጌ ከእስር ተለቀቁ
ማክሰኞ፣ ግንቦት 21 2010ማስታወቂያ
ወደ አራት ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ የቆዩት የተቃዋሚው የግንቦት ሰባት የነጻነት የዴሞክራሲ እና የፍትህ ንቅናቄ ዋና ጸሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ተፈተዋል። ቤተሰቦቻቸው ወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ደጋፊዎቻቸው ዛሬ አቶ አንዳርጋቸው አዲስ አበባ የሚገኘው የአባታቸው ቤት ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አቀባበል ኮሚቴ አስተባባሪ ፖለቲከኛ ዳንኤል ሺበሺ እንደተናገሩት በስፍራው በርካታ ህዝብ ተገኝቶ ነው የተቀበላቸው። አቶ ዳንኤል አቶ አንዳርጋቸው አዲስ አበባ እንደሚቆዩም ነግረውኛል ብለዋል። ከአቶ ዳንኤል ሺበሺ ጋር የተደረገው ቃለ ምልልስ የድምጽ ማዕቀፉን በመጫን ማዳመጥ ይቻላል።
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ