ጥቃት በማእከላዊ ጎንደር
ሰኞ፣ መስከረም 19 2012ማስታወቂያ
በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትናንት ጠዋት ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች በመኪና ይጓዙ በነበሩ ሰዎች ላይ በፈጸሙት ጥቃት የሰዎች ህይወት ማለፉን መንግስትና የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡ ትናንትና ጠዋት ከጭልጋ ወደ መተማ በሚጓዝ ተሸከርካሪ ከነበሩ ተሳፋሪዎች መካከል ግንት በተባለ ቦታ ላይ ታጣቂዎቹ የተሳፋሪዎችን መታወቂያቸውን እያዩ 6ቱን ለይተው እንደገደሏቸው አንድ የጎንደር ከተማ ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ ከጥቃቱ በኋላም የጎንደር ከተማና አካባቢው ወጣቶች ዛሬ ጠዋትና ትናንትና ወደተለያዩ አቅጣጫዎች የሚወስዱ አቢይ መንገዶችን በደንጋይ ዘግተው እንደነበር እና አንድ ሆቴል እንዳወደሙ የአይን እማኙ ለዶየቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከጥቃቱ በኋላ ደረሰ ስለተባለው ግጭት ዝርዝር የምርመራ ውጤት እንዳልደረሰው ለዶቼቬለ አስታውቋል። ዓለምነው መኮንን ከባሕር ዳር ዝርዝር ዘገባ አለው።
አለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ