1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና 

እሑድ፣ መስከረም 11 2012

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና በነበራቸው ቆይታ የኮሎኔል በዛብሕ ጴጥሮስ ጉዳይ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች ስምምነት አንድ አካል እንደሆነ መናገራቸውን በውይይቱ የተሳተፉት የሐዲያ ዞን አስተዳደር የፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን አባይነሕ ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል። 

https://p.dw.com/p/3Q3Nv
Äthiopien | Premier Minister Abiy Ahmed besucht Hosaena
ምስል Ethiopian Prime Minister Office

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና 

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ወደ ሖሳዕና አቅንተው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸው ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል በዞኑ ነዋሪዎች የሚነሳው የክልል አደረጃጀት ጉዳይ፤ የሥራ አጥነት እና የወጣቶች ፍልሰት እና የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ እጣ-ፈንታን የተመለከቱ ጉዳዮች ይገኙበታል። 
ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ጦርነት ወቅት የሚያበሩት ተዋጊ የጦር አውሮፕላን ተመቶ ከወደቀ በኋላ በኤርትራ እጅ የገቡት ከ21 አመታት ገደማ በፊት ነበር። ኮሎኔሉ እስካሁን በሕይወት ስለመኖራቸው ግልፅ ያለ ማረጋገጫ ከኤርትራም ይሁን ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ወገን አልተገኘም። 

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና በነበራቸው ቆይታ የኮሎኔል በዛብሕ ጴጥሮስ ጉዳይ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች ስምምነት አንድ አካል እንደሆነ መናገራቸውን በውይይቱ የተሳተፉት የሐዲያ ዞን አስተዳደር የፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን አባይነሕ ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል።  


ሸዋንግዛው ወጋየሁ
እሸቴ በቀለ