1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጀርመንን የለያየዉ ግንብ አሁንም አለ ይሆን? 

ማክሰኞ፣ ኅዳር 2 2012

ለ 40 ዓመታት በተለያዩ እና በተቃረኑ ስርዓቶች ዉስጥ ይኖሩ የነበሩ ጀርመናዉያን ከተዋሃዱ በኋላ ባለፉት ዓመታት በርካታ ነገሮችን በጋራ ለሃገሪቱ አካሂደዋል። የጀርመኑ ርዕሰ ብሔር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ህሊናችን ዉስጥ ያለዉን የልዩነት ግንብ ልናፈርስ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። ጀርመንን የለያየዉ ግንብ አሁንም አለ ይሆን?

https://p.dw.com/p/3Ssc6
Berlin Gedenkfeier zum Mauerbau
ምስል picture-alliance/AP Photo/M. Schreiber

ዉስጣችን ያለዉ የልዩነት ግንብ ሊፈርስ ይገባል

ለ 40 ዓመታት በተለያዩ እና በተቃረኑ ስርዓቶች ዉስጥ ይኖሩ የነበሩ ጀርመናዉያን ከተዋሃዱ በኋላ ባለፉት ዓመታት በርካታ ነገሮችን በጋራ ለሃገሪቱ አካሂደዋል። ጀርመንን ለሁለት ርዕዮተ ዓለም የከፈለዉ ግንብ ከፈረሰ በኋላ የተለያዩ ቤተሰቦች ዳግም ተገናኝተዋል። ወጣቱ ትዉልድ በአሁኑ ወቅት ምዕራብና ምስራቅ ሳይል ፍቅር መስርቶ ትዳር መስርቶ ይኖራል።  አንድነቱንም ተቀብሎ ምስራቅ ዉስጥ ተዘዋዉሮ ስራ ፈጥሮ ጓደኛና ኃብትን አፍሮቶ መኖር ጀምረዋል። እንድያም ሆኖ ሰሞኑን የወጣ አንድ የጥናት መዘርዝር እንደምያሳየዉ ከፋፋዩ ግንብ ፈረሰ እንጂ አሁንም በአንዳንድ  ጀርመናዉያን ዉስጥ ልዩነት ይታያል። የጀርመኑ ርዕሰ ብሔር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ጀርመንን የከፋፈለዉ ግንብ የፈረሰበት 30ኛ ዓመት በሚታወስት እለት ባሰሙት ንግግር ህሊናችን ዉስጥ ያለዉን የልዩነት ግንብ ልናፈርስ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል ። የእለቱ አዉሮጳና ጀርመን፤ ጀርመንን የለያየዉ ግንብ አሁንም አለይሆን? በሚል ርዕስ የምስራቅና የምዕራብ ጀርመንን የኑሮ ሁኔታ ያስቃኘናል፤ ለመሰናዶዉ የበርሊኑ የዶይቼ ቬለ «DW» ዘጋቢ ይልማ ኃይለሚካኤል ነዉ። 

Symbolbild Wiedervereinigung deutsche Einheit Westdeutsche Ostdeutsche Händedruck
ምስል imago/bonn-sequenz
Deutschland Bundesliga Hertha BSC Berlin v RB Leipzig
ምስል AFP/O. Andersen
Deutschland Bundesliga Hertha BSC Berlin v RB Leipzig
ምስል AFP/O. Andersen

ይልማ ኃይለሚካኤል
አዜብ ታደሰ