1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዶክተር መረራ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 20 2009

ዶክተር መረራ ከጠበቆቻቸዉም ሆነ ከራሳቸዉ የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸዉ ጥያቄ የቀረበ ቢሆንም መርማሪዎች የጀመርነዉ ምርመራ አልተጠናቀቀም በማለታቸዉ ፍርድ ቤቱ ለመጪዉ ጥር 18 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

https://p.dw.com/p/2V1eN
Dr. Merera Gudina Addis Abeba Äthiopien Oromo Pressekonferenz PK
ምስል DW/Y.Egziabhare

Q&A Merera Gudina wird heute vor Gericht gestellt - MP3-Stereo

 
በዛሬዉ ዕለት በፌደራል  የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ የቀጠሮ ችሎት የቀረቡት የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረስ ፕሬዝደንት እና  የመድረክ ምክትል ሊቀመንበር ዶክተር መረራ ጉዲና ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸዉ። ከጠበቆቻቸዉም ሆነ ከራሳቸዉ የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸዉ ጥያቄ የቀረበ ቢሆንም መርማሪዎች የጀመርነዉ ምርመራ አልተጠናቀቀም በማለታቸዉ ፍርድ ቤቱ ለመጪዉ ጥር 18 ቀጠሮ እንደሰጣቸዉ በስፍራዉ የተገኘዉ ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ገልፆልናል። ስለፍርድ ቤት ዉሎዉ አዜብ ታደሰ ዮሐንስን ቀደም ብላ በስልክ አነጋግራዋለች። 

አዜብ ታደሰ

ሸዋዬ ለገሠ