የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ዝግጅት በደቡብ ክልል
ረቡዕ፣ ጥር 19 2013ማስታወቂያ
በኢትዮጲያ የሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመጪው ግንቦት ወር መጨረሻ በሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ የሚሳተፉ አጩ ተወዳዳሪዎችን በመልመል ላይ ናቸው ። አንዳንድ ፓርቲዎችም ለውድድር የመለመሏቸውን እጩዎች ስም ዝርዝርና ፎቶግራፎቻቸውን ከወዲሁ በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴዎቻቸው ማስተዋወቅ ጀምረዋል።እንቅስቃሴውን ከጀመሩት መካከል አንዳንዶቹ ልዩ ልዩ ተግዳሮቶች እንደገጠሟቸው ተናግረዋል።ፖለቲከኞቹ « መጪው ምርጫ በተስፋም በስጋትም የታጀበ ነው» ሲሉ ለዶቼ ቬለ (DW) አስተያየታቸውን አጋርተዋል።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ