የፀጥታ ይዞታ በምሥራቅ ኢትዮጵያ
ሐሙስ፣ ኅዳር 4 2012ማስታወቂያ
በምሥራቅ ኢትዮጵያ የፀጥታ ይዞታው አሳሳቢ መሆኑ እየተነገረ ነው። በድሬደዋ ከሰሞኑ ያገረሸው ግጭት የሁለት ሰዎችን ሕይወት መቀጠፉን፤ በርካቶችም መቁሰላቸውን የድሬደዋ ድል ጮራ ሆስፒታል ለዶቼ ቬለ ገልጿል። በምሥራቅ ሀረርጌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ደግሞ ሁለት አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸው በርካቶችም መጎዳታቸው፤ በአካባቢው የሚገኙ ወገኖችም ስጋት ላይ መውደቃቸውን የአካባቢው ነዋሪ ተናግረዋል። መሳይ ተክሉ ከድሬደዋ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ