1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፀረ ሽብር ሕግ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 14 2011

የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አዲስ መሐመድ እንደሚሉት ተጠርጣሪዎችን «ይሻሻላል» የተባለዉን ፀረ-ሽብር ሕግን ጠቅሶ መክሰስ ተስፋ የተጣለበትን ለዉጥም ሊያደናቅፈዉ ይችላል።

https://p.dw.com/p/3ODXG
Symbolbild Gericht Gesetz Waage und Hammer
ምስል Fotolia/Sebastian Duda

የፀረ ሽብር ሕግ አጠቃቀም

«አፋኝ» ተብሎ የሚወቀሰዉን  የኢትዮጵያ የፀረ-ሽብር ሕግን ጠቅሶ ተጠርጣሪዎችን ማሰርና መክሰስ የፍትሕ ስርዓቱን ለማሻሻል የሚደረገዉን ጥረት የሕዝብ አመኔታ ሊያሳጣዉ እንደሚችል አንዲት የሕግ ባለሙያና ሌላ ጋዘጠኛ መከሩ።የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አዲስ መሐመድ እንደሚሉት ተጠርጣሪዎችን «ይሻሻላል» የተባለዉን ፀረ-ሽብር ሕግን ጠቅሶ መክሰስ ተስፋ የተጣለበትን ለዉጥም ሊያደናቅፈዉ ይችላል።ግዮን የተባለዉ መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሮቤል ምትኩ በበኩሉ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን በፀረ-ሽብር ሕጉ መክሰስ «ስሕተት ነዉ» ይላል።

 ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ