1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጎርፍ አደጋ ያጠቃው አፋር

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 5 2012

በአፋር ክልል የአዋሽ ወንዝ ከተፈጥሯዊ ፍሰቱ ሰብሮ በመውጣት በየዓመቱ የሚያደርሰው ጥፋት በዘላቂነት መፍትሄ እንደሚያስፈልገው ተጠቆመ። ከሰሞኑ በዚሁ መዘዝ ከ67 ሺህ በላይ በጎርፉ ሲጎዳ ከ27 ሺህ የሚበልጥ ሕዝብ መፈናቀሉ ተሰምቷል።

https://p.dw.com/p/3gnu1
Äthiopien | schwere Überschwemmung in Afar
ምስል Allo Yayo

«ከ27 ሺህ ሕዝብ በላይ ተፈናቅሏል»

በአፋር ክልል የአዋሽ ወንዝ ከተፈጥሯዊ ፍሰቱ ሰብሮ በመውጣት በየዓመቱ የሚያደርሰው ጥፋት በዘላቂነት መፍትሄ እንደሚያስፈልገው ተጠቆመ። ከሰሞኑ በዚሁ መዘዝ ከ67 ሺህ በላይ በጎርፉ ሲጎዳ ከ27 ሺህ የሚበልጥ ሕዝብ መፈናቀሉ ተሰምቷል። በጎርፉ ለተጎዱት የዕለት ደራሽ ዕርዳታዎች እየተደረጉ ቢሆንም ከተጎጂዎች ብዛት አኳያ በቂ እንዳልሆነ የክልሉ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ለዶቼ ቬለ አመልክቷል። በተፋሰሱ ላይ ጎርፍ እንዳይመጣ የሚሠሩ ሥራዎች በፌደራል መንግሥት በኩል ትኩረት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ከአዲስ አበባ ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዘገባ አጠናቅሯል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ