1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጉማይዴ ሕዝብ አቤቱታ  

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 16 2013

ተወካዮቹ  የጉማይዴ ሕዝብ ከመጋቢት 2003 ጀምሮ በኮንሶ ዞን ሥር እንዲተዳደር የተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ድምጹን ሲያሰማ መቆየቱን ይናገራሉ። ከ2011 ጀምሮ ከ80 በላይ ሰዎች ሲገደሉ 40 ሺህ ያህል እንደተፈናቀሉ ችግራቸውን ለፌደራል መንግሥት ለማሳወቅ አዲስ አበባ የመጡ የማኅበረሰቡ ተወካዮች ገልጸዋል።

https://p.dw.com/p/3nDca
Äthiopien | Beschwerde der Gumaide Gesellschaft
ምስል Solomon Muche/DW

የጉማይዴ ሕዝብ አቤቱታ

በደቡብ ክልል  የሚገኘው የጉማይዴ ማኅበረሰብ ከፍተኛ የህልውና አደጋ ተጋርጦበታል ሲሉ ተወካዮቹ ተናገሩ። ተወካዮቹ  የጉማይዴ ሕዝብ ከመጋቢት 2003 ዓ/ም ጀምሮ በኮንሶ ዞን ሥር እንዲተዳደር የተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም በሰላማዊ መንገድ በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ድምጹን ሲያሰማ መቆየቱን ይናገራሉ። ከ2011ዓ/ም ጀምሮ ከ 80 በላይ ሰዎች ሲገደሉ 40 ሺህ ያህል እንደተፈናቀሉ፣ ችግራቸውን ለፌደራል መንግሥት ለማሳወቅ አዲስ አበባ የመጡ የማኅበረሰቡ ተወካዮች ተናግረዋል። ጉዳዩን የሚያጣራ ቡድን መላኩን ያሳወቀው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንም ሰዎች በአካባቢው በአሰቃቂ መንገድ መገደላቸውንና ንብረቶችም መውደማቸውን ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።  ሰሎሞን ሙጩ ከአዲስ አበባ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል።
ሰሎሞን ሙጪ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ