1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዶክተር ዐብይ እና የምሁራን ውይይት

ሰኞ፣ ሐምሌ 16 2010

በተለያየ ምክንያት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተባረሩ 42 ምሁራንን ለመመለስ መንግሥት ዝግጁ መሆኑንም ዶክተር ዐብይ ተናግረዋል። ዶቼቬለ ካነጋገራቸው ተሳታፊዎች አንዱ ውይይቱን « ግልጽ እና ውጤታማ»  ብለውታል። እንደረኩበትም ተናግረዋል። ሌላው አስተያየት ሰጭ ደግሞ የተነሱት ጥያቄዎች «ምሁራዊም ሆነ አገራዊ አይደሉም»ሲሉ ነቅፈዋል።

https://p.dw.com/p/31whj
Äthiopien | 3175 Akademiker von 50 äthiopischen Universitäten
ምስል Chief of Staff/Prime Minister Office Ethiopia/F. Arega

የዶክተር ዐብይ እና የምሁራን ውይይት

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ዛሬ ከ50 የተለያዩ ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማት ከተወከሉ ሦስት ሺህ አንድ መቶ ሰባ አምስት 3175 መምህራን ጋር የካሄዱት ውይይት በተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥቶበታል። መምህራኑ በውይይቱ ወቅት ላነሷቸው የተለያዩ ጥያቄዎች  ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ሰጥተዋል።  በተለያየ ምክንያት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተባረሩ 42 ምሁራንን ለመመለስ መንግሥት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል። ዶቼቬለ ካነጋገራቸው ተሳታፊዎች አንዱ ውይይቱን « ግልጽ እና ውጤታማ»  ብለውታል። እንደረኩበትም ተናግረዋል። ሌላው አስተያየት ሰጭ ደግሞ የተነሱት ጥያቄዎች «ምሁራዊም ሆነ አገራዊ አይደሉም»ሲሉ ነቅፈዋል። ይልቁንም በዩኒቨርስቲ ደረጃ ሊፈቱ የሚችሉ እንደነበሩ እና በውይይቱም እንዳልተደሰቱ የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ገልጸዋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር 
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ