1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የድንበር ተሻጋሪ ሾፌሮች ቅሬታ 

ዓርብ፣ ግንቦት 21 2012

የጤና ሚኒስቴር በኮሮና ተኅዋሲ የሚያዙ ሰዎችን ሲገልጽ የእኛን ሙያ ጠቅሶ ሪፖርት ማድረጉ የምናጓጉዘውን ሸቀጥ በምናቀርብለት ማህበረሰብ እንድንገፋ እያደረገን በመሆኑ ሊታረም ይገባል ብለዋል።መንግስት በበኩሉ እነዚህ አሽከርካሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ከበሽታው እንዲጠበቁ በቀጣይ ስራዎች ይከናወናሉ ብሏል

https://p.dw.com/p/3czXO
Äthiopien Straße Ababa-Djibouti
ምስል DW/Y. Gebregziabher

የድንበር ተሻጋሪ ሾፌሮች ቅሬታ

በስራችን ምክንያት ጅቡቲ ደርሰን ስንመለስ ህብረተሰቡ በቤተሰቦቻችን ላይ ሳይቀር መገለል እየደረሰብን ነው ሲሉ የድንበር ተሻጋሪ ከባድ መኪና ሾፌሮች ተናገሩ።በተለይ የጤና ሚኒስቴር በኮሮና ተኅዋሲ የሚያዙ ሰዎችን ሲገልጽ የእኛን ሙያ ጠቅሶ ሪፖርት ማድረጉ የምናጓጉዘውን ሸቀጥ በምናቀርብለት ማህበረሰብ እንድንገፋ እያደረገን በመሆኑ ሊታረም ይገባል ብለዋል።
መንግስት በበኩሉ እነዚህ አሽከርካሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ከበሽታው እንዲጠበቁ በቀጣይ ስራዎች ይከናወናሉ ብሏል።ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ 
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ