የድምፃዊ ኑሆ ጎበና ስርዓተ ቀብር
ሐሙስ፣ ጥር 12 2014ማስታወቂያ
በኦሮምኛ ቋንቋ ሙዚቃዎቹ ስምና ዝና ያተረፈዉ ድምፃዊ ኑሆ ጎበና ዛሬ አዳማ ዉስጥ ተቀበረ።ኑሆ ያረፈዉ ከትናንት በስቲያ በሕክምና እየተረዳ ነዉ።68 ዓመቱ ነበር።በዛሬዉ የቀብር ሥርዓት ላይ ቤተ-ሰቦቹ፣ ዘመድ ወዳጆቹ፣ የስራ ባልደረቦቹና አድናቂዎቹ ተገኝተዋል።አንድነትን በሚያወድሱ ዘፈኖቹ የሚታወቀው ኑሆ ከ1970ዎቹ ጀምሮ ህዝብን በሚያነቃቁ የትግል ዘፈኖቹም እንደሚታወቅ የስራ ባልደረቦቹ ይመሰክራሉ፡፡
ስዩም ጌቱ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ