የዱባይ የምግብ ዐውደ ርዕይ
ረቡዕ፣ የካቲት 11 2012ማስታወቂያ
25ተኛው ዓለም አቀፉ «ገልፍ ፉድ« የተባለው የምግብ ምርት የሚተዋወቅበት ዓመታዊ ዐውደ ርዕይ ካለፈው እሁድ ጀምሮ በተባበሩት አረብ ኤምሬትዋ በዱባይ ከተማ እየተካሄደ ነው። በዚሁ ዐውደ ርዕይ ላይ በርካታ የኢትዮጵያ ኩባንያዎች ልዩ ልዩ የግብርና ምርቶቻቸውን እያስተዋወቁ እና እየሸጡም ነው።በዐውደ ርዕዩ ከሚካሄደው ሽያጭ ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የኢትዮጵያ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።የዛሬው ከኤኮኖሚው ዓለም ዝግጅታችን በዱባዩ ዐውደ ርዕይ ላይ ያተኩራል።ያዘጋጀው እንዳልካቸው ፈቃደ ያቀርብልናል።
እንዳልካቸው ፈቃደ
ኂሩት መለሰ