1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደቡብ ክልል ጉባኤ

ዓርብ፣ መጋቢት 9 2014

እስካሁን የሲዳማና እንዲሁም አምስት ዞኖችና አንድ ልዩ ወረዳን ያካተተው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች በሕዝበ ውሳኔ ራሳችውን በቻሉ ክልሎች ቢደራጁም የተቀሩት ዞኖች ግን አሁንም ምላሽ እየጠበቁ ይገኛሉ፡፡

https://p.dw.com/p/48hFN
General assembly SNNPR, Äthiopien
ምስል Shewangizaw Wehgayehu/DW

የክልሉ ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤ

በደቡብ ክልል የሚነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎችን ለመመለስ እየሠራ እንደሚገኝ የክልሉ ምክር ቤት አስታወቀ። የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ሰርሞላ ይኽን የተናገሩት ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተጀመረው የምክር ቤቱ ስድስተኛ ዙር አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው። አፈ ጉባኤዋ በመክፈኛ ንግግራቸው በክልል ለመደራጀት ጥያቁ ያቀረቡ ሕዝቦች ባልተረጋገጠ ወሬ እና ውዥንብር ሳይደናገሩ ምላሹን በትዕግሥት ሊጠብቁ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ 

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ