1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደቡብ ሱዳን ማስተባበያ 

ማክሰኞ፣ ጥር 9 2009

ሦስቱ ሀገራት ኢትዮጵያን የሚደግፈውን የሱዳን መንግሥት ለመገልበጥ ለሚታገሉ ታጣቂዎች ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች ለመክፈት መስማማታቸውን ሱዳን ትሪብዩን ጋዜጣው ዘግቧል። ደቡብ ሱዳን ግብጽ እና ዩጋንዳ ለሱዳን ተቃዋሚዎች ማሰልጠኛ ጣቢያ ለማቋቋም ተስማምተዋል ተብሎ የቀረበውን ዘገባ ደቡብ ሱዳን አስተባበለች።

https://p.dw.com/p/2Vw2z
Äthiopien Südsudanischer Botschafter James Pitia Morgan
ምስል DW/Getacjew Tedla HG

Beri AA (South Sudans Anbasador briefing on Sudan Tribune's reporting) - MP3-Stereo

በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጀምስ ፒትየ ሞርጋን አዲስ አበባ ውስጥ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የተሰራጨው ዜና ሀሰት ነው ብለዋል። ሱዳን ትሪብዩን የተባለው ጋዜጣ  ባለፈው ሳምንት  ባወጣው ዘገባ የሦስቱ ሃገራት መሪዎች፣ በአባይ ወንዝ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ የምትገነባውን ኢትዮጵያን የሚደግፈውን የሱዳን መንግሥት ለመገልበጥ ለሚታገሉ ታጣቂዎች ዩጋንዳ እና ደቡብ ሱዳን ድንበር ላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች ለመክፈት መስማማታቸውን ተችዎችን ጠቅሶ ዘግቧል። ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን ልኮልናል ።   

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ


ኂሩት መለሰ 

ሸዋዬ ለገሠ