1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩክሬን ሩሲያ ፍጥጫና የጦርነት ስጋት 

ረቡዕ፣ የካቲት 16 2014

ሩሲያ ከዩክሬን ለመገንጠል ለሚንቀሳቀሱ ሁለት ግዛቶች እውቅና መስጠቷ በሁለቱ ሃገራት መካከል የተጀመረው እሰጥ አገባ ይበልጥ አክርሮታል። ምዕራቡ ዓለም በሩሲያ ላይ ጫና ለማሳደር የሚወስዳቸው የማዕቀብ ርምጃዎች ሁኔታውን እንዳያባብሱት የሚሰጉ አሉ።

https://p.dw.com/p/47UhZ
Ukraine-Konflikt | Lage in Ostukraine | Region Rostow Donezk
ምስል AA/picture alliance

የጦርነት ሥጋት እና ቀዝቃዛው ጦርነት

የሩሲያ ወረራ ያሰጋኛል ያለችው ዩክሬን ለ30 ቀናት የሚዘልቅ የአስጠኳይ ጊዜ አዋጅ ለመደንገግ መዘጋጀቷ ተሰምቷል። በድንጋጌው መሠረት ዩክሬናውያን በቤት ተወስነው እንዲቆዩ ወይም የሰዓት እላፊ ሊከተል እንደሚችል ተገምቷል።  ሩሲያ ከዩክሬን ለመገንጠል የሚንቀሳቀሱ ሁለት ግዛቶች እውቅና መስጠቷ በሁለቱ ሃገራት መካከል የተጀመረው እሰጥ አገባ ይበልጥ አክርሮታል እየተባለ ነው። ሩሲያ ከዩክሬን ለመገንጠል የሚንቀሳቀሱ አማጽያንን መደገፏን የተቃወመው የአውሮጳ ሕብረት ማዕቀብ የጣለ ሲሆን ከአሜሪካ ወገንም ተመሳሳይ ርምጃዎች መኖራቸው ተገልጿል።  ምዕራቡ ዓለም በሩሲያ ላይ ጫና ለማሳደር የሚወስዳቸው የማዕቀብ ርምጃዎች ሁኔታውን እንዳያባብሱት የሚሰጉ አሉ። 

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ