1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ትምህርትአፍሪቃ

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከትግራይ ወጡ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 11 2013

ትግራይ ዉስጥ የሚደረገዉ ጦርነት ያሰጋቸዉ የተማሪዎቹ  ወላጆችና ቤተሰቦች፣ መንግስትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተማሪዎቹን ከክሉ ያስወጡላቸዉ ዘንድ በአደባባይ ሰልፍ ጭምር ጠይቀዉ ነበር።ይሁንና በፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ተማሪዎቹ በተፈለገዉ ፍጥነት ከትግራይ ክልል አለመዉጣታቸዉ ሥጋት አስከትሎ ነበር።

https://p.dw.com/p/3z5te
Äthiopien | Logo of Ministry of Science and Higher Education

ከ10 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ከየቤተሰቦቻቸዉ ተቀላቅለዋል

በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ወደየ ቤተሰቦቻቸው መሸኘታቸውን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በሳምንቱ ማብቂያ አሳውቋል።ትግራይ ዉስጥ የሚደረገዉ ጦርነት ያሰጋቸዉ የተማሪዎቹ  ወላጆችና ቤተሰቦች፣ መንግስትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተማሪዎቹን ከክሉ ያስወጡላቸዉ ዘንድ በአደባባይ ሰልፍ ጭምር ጠይቀዉ ነበር።ይሁንና በፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ተማሪዎቹ በተፈለገዉ ፍጥነት ከትግራይ ክልል አለመዉጣታቸዉ ሥጋት አስከትሎ ነበር።የሳይስና ከፍተኛ ትምሕርት ሚኒስቴር ባለፈዉ ሳምንት አርብ እንዳስታወቀዉ ግን ካለፈዉ ሐምሌ መጀመሪያ ጀምሮ መቀሌ፣አዲግራት፣ አክሱምና ራያ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ከ10 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ከየአካባቢዉ ወጥተዋል።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ