የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ተፈናቃዮች ሮሮ
ዓርብ፣ መስከረም 14 2014ማስታወቂያ
ከአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ተፈናቅለው ባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ 2000 ያህል ተፈናቃዮች ህብረተሰቡ ከሚያደርግልን እገዛ ውጪ መንግስት ያለንበትን ሁኔታ እንኳ አያውቅም ሲሉ ቅሬታቸውን ገለፁ። የተፈናቃዮች ሀብት አሰባሰብ ኮሚቴ ግን ከመንግስት የቀለብ ድጋፍ መደረጉን ተናግሯል። የክልሉ አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን አንድ የስራ ኃላፊም እርዳታው እንደቤት ባይሆንም እየታገዙ አንደሆነ ገልጠዋል፡፡ የባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎችም የምግብና የአልባሳት ድጋፍ አድርገዋል፣ እያደረጉም ነው፡፡
ዓለምነው መኮንን
አዜብ ታደሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ