የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 13 2014ማስታወቂያ
የአፍሪካ ሕብረት ኢትዮጵያን በተመለከተ እስካሁን የተከተለውን መርሕ የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር "ገንቢ" በማለት አወደሰዉ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የሕብረቱ የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ተፋላሚ ኃይላትን ለመሸምገል የሚያደርጉትን ጥረት ኢትዮጵያ እንደምትደግፍ አስታዉቀዋል።አምባሳደር ዲና እንዳሉት የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን የመንግስታቸዉን አድናቆትና ድጋፍ ለሕብረቱ የሰላምና የፀጥታ የበላይ ኃላፊ ገልፀዋል።
ሰሎሞን ሙጬ
ነጋሽ መሐመድ
እሸቴ በቀለ