የኮንሶ ተመላሾች ችግርና ስጋት
ሐሙስ፣ ጥር 27 2013ማስታወቂያ
በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን ለወራት በተከሰተው ግጭት መንደራቸውን ጥለው ከሸሹት 84 ሺህ ተፈናቃዮች መካከል አብዛኞቹን ወደ ቀደመ ቀዬቸው የመመለስ ስራ ማከናወኑን የዞኑ መስተዳድር አስታወቀ።በመሬት ይገባኛልና በወረዳ መዋቅር ጥያቄ ሳቢያ ለወራት በግጭት ሲናጥ የከረመው የኮንሶ አካባቢ አሁን አንጻራዊ መረጋጋት እየሰፈነበት መምጣቱን የፀጥታ ባለስልጣናት ገልጸዋል ።አስተያየታቸውን ለዶቼ ቬለ (DW) የሰጡ ተመላሽ የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው ከምግብና መጠለያ አጦት በተጨማሪ ግጭቱ ዳግም ሊያገረሽ ይችላል የሚል ስጋት እንዳለባቸው ይናገራሉ።
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ