የኮሮና ወረርሽኝ ከአንድ አመት በኋላ በአፍሪካ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 7 2013ማስታወቂያ
ከአንድ አመት በፊት መጋቢት 2 ቀን 2012 ዓ.ም. የዓለም ጤና ድርጅት ኮሮና ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ሆኗል ብሎ ሲያውጅ በአፍሪካ በተሕዋሲው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 47 ብቻ ነበር። ከአንድ አመት በኋላ በአፍሪካ አራት ሚሊዮን ገደማ ሰዎች በወረርሽኙ መያዛቸውን የአፍሪካ የበሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ማዕከል ባለፈው ሳምንት ይፋ አድርጓል።
ከ106,000 በላይ ሰዎች ደግሞ ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን አጥተዋል።ይሁንና የሕክምና ባለሙያዎችን ጨምሮ በርካቶች በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከዚህም ሊልቅ እንደሚችል ጥርጣሬ አላቸው። በዛሬው የጤና እና አካባቢ ዝግጅት ሲልጃ ፍሮሕሊሽ ወረርሽኙ በአፍሪካ በአንድ አመት ዉስጥ ስላደረሰዉ ጉዳት የዘገበችዉን ይልማ ኃይለ ሚካኤል አጠናቅሮታል።
ሲልጃ ፍሮህሊሽ/ይልማ ኃይለሚካኤል
እሸቴ በቀለ